እግዚአብሔር ይናገራል 1
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (27)
13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ቸ)
22. የሰውን ምሥጢር ለማወቅ አትከጅል
ሰዎች እንዳንተ ናቸው ። አካላዊ መዋቅራቸው ከአንተ ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ሁሉ ውስጣዊ ስሜታቸውም ተመሳሳይ ነው ። ሰውን ከሰው ልዩ የሚያደርገው ችግሮችን የሚፈታበት ጥበቡ ፣ ነገሮችን የሚቀበልበት ልቡ ነው ። ከዛሬ ሦስት ሺህ ዓመት በፊት የተጻፈ ምክር ዛሬ ላይ የሚሠራው በዚያ ዘመን ከነበሩት ሰዎች ጋር የኑሮ ዝምድና ስላለን ፣ ተመሳሳይ የሕይወት ገጽታ ስለምናስተናግድ ነው ። በሥልጣኔ ብንለያይም በመወለድ ፣ በማደግ ፣ በሞት ሕግ ተመሳሳይ ነን ። ሁላችንም ለመኖር እንበላለን ። ደስታችንም በሌሎች ጉድለት ውስጥ ተቀምጧል ። የሌሎችን ጉድለት ስንሞላ የእኛን ደስታ እንቀበላለን ። ሰዎች የራሳቸው ምሥጢር እንዲኖራቸው መፍቀድ ያስፈልግሃል ። ሚስትህም ልጆችህም ካንተ ጋር አንድ አካልና የአካል ክፋይ ቢሆኑም የራሳቸው ግላዊ ሕይወት እንዳላቸው ማመን ያስፈልግሃል ። ወደው ፈቅደው እስኪያሳውቁህ ድረስ ቀና ሰው መሆን አለብህ ።
መንፈሳዊ አገልጋይና ካህን በሆንህ ጊዜ እንደ መርማሪ ፖሊስ የሰዎችን ኃጢአት ለማወቅ አትፈልግ ። ኑዛዜ ማለት ሰዎች ፈቅደው የተናገሩት ስህተት እንጂ እኛ ለማወቅ ያደረግነው ጥረትና ውጤት አይደለም ። የሰዎችን ገመና ተገልጦ ባየህ ጊዜ ለማየት አትጓጓ ። ስለሌሎች አንተ ጋ ሲወራ ፣ ስላንተ ደግሞ ሌሎች ጋ እየተወራ ነው ። ስላልሰማነው እንጂ ሁላችንም ስም አለን ። የሰው ልጅ ሥራ ሲፈታ እንኳን መሰሉን ድንጋይንም ያማል ። ሰዎች ወደው ፈቅደው የነገሩህን በጸሎተኛ ልብ ስማ ። አንዳንድ ችግር እየጸለዩ ካልሰሙት የአሳብ ውጊያ የመንፈስ ትግል ይፈጥራልና ። ችግሩን ከሰማህ በኋላ ስሜታቸውን ተካፈለው ። ነገር ግን ያለ ምክር አትስደዳቸው ። ወዳጅህ በለመነህ ጊዜ ሳንቲም ማጣትህ ይቆጫል ። ለአንድ ቀን እንኳ አልሆንኩትም ያሰኛል ። ሰዎች ባማከሩህ ጊዜ ምክር ካጣህ በመጡበት ስሜት ይመለሳሉ ። ምክር እንዲኖርህ ተመከር ። መምህራንን ተወዳጅ ፣ መጻሕፍትን ቤተ ዘመድህ አድርግ ። ከዚህች ሰዓት በኋላ የመኖር አቅም ላይኖራቸው ይችላልና ዝም ብለህ አትሸኛቸው ።
አንዳንድ ሰዎች በራሳቸውና በቤታቸው ምን እየሆነ እንዳለ አያውቁም ። ሳያውቁት ወደ ድብርት ውስጥ እየገቡ ነው ። አካላዊና ሥነ ልቡናዊ መታወክ እየደረሰባቸው ነው ። የላኛው አካል የውስጠኛውን ሰውነት በጥቂቱም ቢሆን ይናገራል ። ይልቁንም ፊት የልብ አደባባይ ነውና ፊታቸውን አይተህ ልባቸውን ለማወቅ ይቻልሃል ። ጨዋታቸው ሲቀንስ ፣ መሄድ ሲያቅታቸው ፣ ላለመደሰት ሲሞክሩ ፣ ሁሉንም ነገር በዜሮ ሲያባዙ ፣ ከሰው ሲሸሹ ፣ ምሬት ሲያበዙ ፣ … አንድ ችግር ውስጥ እንዳሉ ምልክት ነው ። በዚህ ጊዜ በዘዴ ማማከር ይገባል ። አንዳንድ ጊዜ ምን ሆነሃል ብሎ መጠየቅ ይቻላል ። ሌላ ጊዜ ደግሞ ዙሪያ ገባውን በወሬ በማነሣሣት ሰውዬው ራሱ የውስጡን እንዲናገር መርዳት ይገባል ።
የሰዎችን ምሥጢር ለማወቅ የምሻው ለምንድነው ? ብለህ ራስህን ጠይቅ ። የሰማሁትን ምን መፍትሔ ሰጥቼዋለሁ ብለህ ራስህን ገምግም ። ምሥጢር የማወቅ ጥማት አንድ ቀን የማይሸከሙት አደጋ ላይ ይጥላል ። የደኅንነት ሠራተኞች ለመንግሥታቸው ጆሮ ሆነው ምሥጢር ቢያነፈንፉ ደመወዝተኞች ስለሆኑ ነው ። በነጻ ምሥጢርን ማነፍነፍ ግን ወሬ መውደድ ነው ። “እሺ እባክህ” ፣ “ተው እንጂ” ፣ “ይገርማል” ፣ “አያድርስ ነው” ፣ … የሚሉ ቃላት የወሬ ነዳጅ ናቸው ። ምሥጢሩ የሚያድን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ማወቅና መፈጸም እርሱ የሐዲሱ ኪዳን በር ነው ።
የሰዎችን ምሥጢር ማወቅ መፈለግ ከአንተ ጋር የሚመሳሰል ሰው አግኝቶ ለመረጋጋት ነው። አንተ የምትሠራውን ኃጢአት የሚሠራ ከሆነ ብቻዬን አይደለሁም ብሎ ለመደሰት ነው ። አንድን ነገር ስትፈልግ ለምንድነው የምፈልገው ? ብለህ ራስህን ጠይቅ ። ነገር ግን መፍትሔ ፈላጊ ወንበር ላይ ስትቀመጥ ሰዎችን እየጠየቅህ ፈውስና መልስ ማዘጋጀት ሙያ ነው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም.
13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ቸ)
22. የሰውን ምሥጢር ለማወቅ አትከጅል
ሰዎች እንዳንተ ናቸው ። አካላዊ መዋቅራቸው ከአንተ ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ሁሉ ውስጣዊ ስሜታቸውም ተመሳሳይ ነው ። ሰውን ከሰው ልዩ የሚያደርገው ችግሮችን የሚፈታበት ጥበቡ ፣ ነገሮችን የሚቀበልበት ልቡ ነው ። ከዛሬ ሦስት ሺህ ዓመት በፊት የተጻፈ ምክር ዛሬ ላይ የሚሠራው በዚያ ዘመን ከነበሩት ሰዎች ጋር የኑሮ ዝምድና ስላለን ፣ ተመሳሳይ የሕይወት ገጽታ ስለምናስተናግድ ነው ። በሥልጣኔ ብንለያይም በመወለድ ፣ በማደግ ፣ በሞት ሕግ ተመሳሳይ ነን ። ሁላችንም ለመኖር እንበላለን ። ደስታችንም በሌሎች ጉድለት ውስጥ ተቀምጧል ። የሌሎችን ጉድለት ስንሞላ የእኛን ደስታ እንቀበላለን ። ሰዎች የራሳቸው ምሥጢር እንዲኖራቸው መፍቀድ ያስፈልግሃል ። ሚስትህም ልጆችህም ካንተ ጋር አንድ አካልና የአካል ክፋይ ቢሆኑም የራሳቸው ግላዊ ሕይወት እንዳላቸው ማመን ያስፈልግሃል ። ወደው ፈቅደው እስኪያሳውቁህ ድረስ ቀና ሰው መሆን አለብህ ።
መንፈሳዊ አገልጋይና ካህን በሆንህ ጊዜ እንደ መርማሪ ፖሊስ የሰዎችን ኃጢአት ለማወቅ አትፈልግ ። ኑዛዜ ማለት ሰዎች ፈቅደው የተናገሩት ስህተት እንጂ እኛ ለማወቅ ያደረግነው ጥረትና ውጤት አይደለም ። የሰዎችን ገመና ተገልጦ ባየህ ጊዜ ለማየት አትጓጓ ። ስለሌሎች አንተ ጋ ሲወራ ፣ ስላንተ ደግሞ ሌሎች ጋ እየተወራ ነው ። ስላልሰማነው እንጂ ሁላችንም ስም አለን ። የሰው ልጅ ሥራ ሲፈታ እንኳን መሰሉን ድንጋይንም ያማል ። ሰዎች ወደው ፈቅደው የነገሩህን በጸሎተኛ ልብ ስማ ። አንዳንድ ችግር እየጸለዩ ካልሰሙት የአሳብ ውጊያ የመንፈስ ትግል ይፈጥራልና ። ችግሩን ከሰማህ በኋላ ስሜታቸውን ተካፈለው ። ነገር ግን ያለ ምክር አትስደዳቸው ። ወዳጅህ በለመነህ ጊዜ ሳንቲም ማጣትህ ይቆጫል ። ለአንድ ቀን እንኳ አልሆንኩትም ያሰኛል ። ሰዎች ባማከሩህ ጊዜ ምክር ካጣህ በመጡበት ስሜት ይመለሳሉ ። ምክር እንዲኖርህ ተመከር ። መምህራንን ተወዳጅ ፣ መጻሕፍትን ቤተ ዘመድህ አድርግ ። ከዚህች ሰዓት በኋላ የመኖር አቅም ላይኖራቸው ይችላልና ዝም ብለህ አትሸኛቸው ።
አንዳንድ ሰዎች በራሳቸውና በቤታቸው ምን እየሆነ እንዳለ አያውቁም ። ሳያውቁት ወደ ድብርት ውስጥ እየገቡ ነው ። አካላዊና ሥነ ልቡናዊ መታወክ እየደረሰባቸው ነው ። የላኛው አካል የውስጠኛውን ሰውነት በጥቂቱም ቢሆን ይናገራል ። ይልቁንም ፊት የልብ አደባባይ ነውና ፊታቸውን አይተህ ልባቸውን ለማወቅ ይቻልሃል ። ጨዋታቸው ሲቀንስ ፣ መሄድ ሲያቅታቸው ፣ ላለመደሰት ሲሞክሩ ፣ ሁሉንም ነገር በዜሮ ሲያባዙ ፣ ከሰው ሲሸሹ ፣ ምሬት ሲያበዙ ፣ … አንድ ችግር ውስጥ እንዳሉ ምልክት ነው ። በዚህ ጊዜ በዘዴ ማማከር ይገባል ። አንዳንድ ጊዜ ምን ሆነሃል ብሎ መጠየቅ ይቻላል ። ሌላ ጊዜ ደግሞ ዙሪያ ገባውን በወሬ በማነሣሣት ሰውዬው ራሱ የውስጡን እንዲናገር መርዳት ይገባል ።
የሰዎችን ምሥጢር ለማወቅ የምሻው ለምንድነው ? ብለህ ራስህን ጠይቅ ። የሰማሁትን ምን መፍትሔ ሰጥቼዋለሁ ብለህ ራስህን ገምግም ። ምሥጢር የማወቅ ጥማት አንድ ቀን የማይሸከሙት አደጋ ላይ ይጥላል ። የደኅንነት ሠራተኞች ለመንግሥታቸው ጆሮ ሆነው ምሥጢር ቢያነፈንፉ ደመወዝተኞች ስለሆኑ ነው ። በነጻ ምሥጢርን ማነፍነፍ ግን ወሬ መውደድ ነው ። “እሺ እባክህ” ፣ “ተው እንጂ” ፣ “ይገርማል” ፣ “አያድርስ ነው” ፣ … የሚሉ ቃላት የወሬ ነዳጅ ናቸው ። ምሥጢሩ የሚያድን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ማወቅና መፈጸም እርሱ የሐዲሱ ኪዳን በር ነው ።
የሰዎችን ምሥጢር ማወቅ መፈለግ ከአንተ ጋር የሚመሳሰል ሰው አግኝቶ ለመረጋጋት ነው። አንተ የምትሠራውን ኃጢአት የሚሠራ ከሆነ ብቻዬን አይደለሁም ብሎ ለመደሰት ነው ። አንድን ነገር ስትፈልግ ለምንድነው የምፈልገው ? ብለህ ራስህን ጠይቅ ። ነገር ግን መፍትሔ ፈላጊ ወንበር ላይ ስትቀመጥ ሰዎችን እየጠየቅህ ፈውስና መልስ ማዘጋጀት ሙያ ነው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም.
እግዚአብሔር ይናገራል 2
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
የዘመናችን ፈተና ዲ/ን አሸናፊ መኮንን part 11 Ye Zemenachen Fetena Part 11 Deacon As...
https://youtube.com/watch?v=z68HD-tDRvk&si=62Z9QlAy-BjdaRbh
https://youtube.com/watch?v=z68HD-tDRvk&si=62Z9QlAy-BjdaRbh
YouTube
የዘመናችን ፈተና ዲ/ን አሸናፊ መኮንን part 11 Ye Zemenachen Fetena Part 11 Deacon Ashenafi Mekonnen
To subscribe https://www.youtube.com/user/StGebrielTechGroup?sub_confirmation=1
Website: www.finotewongel.org
Facebook: https://www.facebook.com/%E1%8D%8D%E1%8A%96%E1%89%B0-%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8C%8C%E1%88%8D-Finote-Wongel-121675515154285
Website: www.finotewongel.org
Facebook: https://www.facebook.com/%E1%8D%8D%E1%8A%96%E1%89%B0-%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8C%8C%E1%88%8D-Finote-Wongel-121675515154285
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (28)
14. ቀጠሮ አክብር
ቀጠሮ የተጀመረው በእግዚአብሔር ነው ። ይህ ዓለም በመለኮታዊ ቀጠሮ የተፈጠረ ዓለም ነው ። ዘመን የሌለው ጌታ ዘመንን ለሰዎች ሰጠ ። ሰው በበደል በወደቀ ጊዜ ለመዳን ቀጠሮ ተሰጠው ። ሰው ከእግዚአብሔር ሳይለይ ከእግዚአብሔር ተለየ ። ለሆዱ እንጀራን ፣ ለአፍንጫው እስትንፋስን የሚያገኘው ከእግዚአብሔር ነው ። እንኳን በምድር በሲኦልም የሚኖረው በእግዚአብሔር ሕይወት ነው ። ጌታችን ወደ ምድር የመጣው ለሰዎች እንጀራ ለመስጠት ሳይሆን ራሱ ኅብስተ ሕይወት መሆኑን ለመግለጥ ነው ። 5500 ዘመን ሰው እንጀራ እየበላ ነበር ። ነፍሱ ግን ስደተኛና ረሀብተኛ ነበረች ። ሰው እግዚአብሔርን የሚክደው ከእግዚአብሔር የተቀበለውን እስትንፋስ መልሶ ሳይሆን በእግዚአብሔር ሕይወት ላይ ቆሞ ነው ። “በማን ላይ ቆመሽ ማንን ታሚያለሽ!” ይባላል ። እርሱ የካዱትን ቢክድ ኖሮ ፍጥረት በምድር ላይ ባልቆየ ነበር ። እግዚአብሔር ቀጠሮን መጀመሩ ብቻ ሳይሆን የሺህ ዘመናት ቀጠሮን የሚሰጥ አምላክ ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ ከሚኖረው ዕድሜ የረዘመ ቀጠሮ ተሰጠው ። ይህ ብዙ ፍቺ አለው ። የመጀመሪያው የሰው የህልውናው መጨረሻ መቃብር አይደለም ። በሥጋው ያጣውን በነፍሱ ሊክሰው የሚችል አምላክ አለው ። ዛሬ በሥጋ ጉድለታችን ስንፈራ ስንጨነቅ ጌታ ግን አይጨነቅም ። ምክንያቱም በሰማይም ሊጋብዘን ይችላልና።
እኛ ምንም ሳናደርግላቸው የሄዱት ወገኖቻችን የእግር እሳት ሆነውብን ይሆናል ። ደግነታችንን መቃብር ገድቦት ይሆናል ። በሰማያዊው ዓለምም የሚሰጥ አምላክ ግን ሞት ገደቡ አይደለም ። ከሰው ዕድሜ የሚረዝመው ቀጠሮ ለምን ተሰጠ ካልን ከ5500 ዘመን በኋላም የሚኖረው ሰው አዳም ስለሆነ ነው ። ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ ያላቸው እስከ ዓለም ፍጻሜ የሚኖሩ ሆነው አይደለም ። የእነርሱን ሥራ የሚያስቀጥል ሁሉ ሐዋርያ ስለሆነ በደቀ መዛሙርቶቻችሁ ላይ አድሬ እሠራለሁ ማለቱ ነው ። ስለዚህ ጴጥሮስ ይህን ሲሰማ ብሞትም ሕያው ነኝ ፤ የመንፈስ ልጅ አለኝ ብሎ ይጽናናል ። የአዳምን ቀጠሮ ክርስቶስ ሲሰቀል የነበሩ ሁሉ ፍጻሜውን አይተዋል ። አንድ አዳም ነን ። አንድ ስለሆንን የአዳም በደሉና ጥፋቱ አግኝቶናል ። የአዳም መዳኑና ካሣው ነጻ አውጥቶናል ። በሞት አንድ ሁነን በኑሮ መለያየታችንና መከፋፋታችን ይገርማል ።
የእግዚአብሔርን ቀጠሮ ልዩ የሚያደርገው የማይረሳ አምላክ መሆኑ ነው ። እኛ ቀጠሮአችንን በመርሳት ፣ ባለመመቸት ፣ ባለመፈለግ ፣ በመስጋት ፣ ሌላውን ጉዳይ በማስበለጥ እንሰርዛለን ። እግዚአብሔር ግን መርሳት የሌለበት የሕሊናት ሁሉ ባለቤት ነው ። አይመቸውም አይባልም ፣ እርሱ የሌለውን ና ብሎ መጥራት የሚችል አምላክ ነው ። በሰጠው ተስፋ አይጸጸትምና አልፈልጋችሁም አይለንም ። የሚሽረው የለምና አይሰጋም ። የዘላለም ጉዳዩ እኛ ነንና የእርሱ ውዶች ነን ። እግዚአብሔር ቀጠሮን የሚያከብር አምላክ ነው ። የእርሱ ተከታዮች እርሱን ይመስላሉና ቀጠሮን ያከብራሉ ። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤” ገላ 4፡4 ።
አንተም ቀጠሮ መስጠትን ልመድ ። ምክንያቱም አንተ እንደ ተመቸህ ያ ሰው አይመቸውምና በድንገት ውረድ ፍረድ አትበል ። ዓመት ሙሉ የረሳኸውን ሰው ዛሬ ስታገኘው አልላቀቅህም ብለህ ስሜታዊ አትሁን ። ቀጠሮ መስጠት ለሰውዬው ምቾት ፣ ለጉዳዩ ክብደት ነው ። ቀጠሮ በሰጠህ ጊዜ ወዳጅህ ተኝቶ እንዲያድር ወይም ተዘጋጅቶ እንዲመጣ ርእሱን ንገረው ። የምፈልግህ በዚህ ምክንያት ነው ብለህ አሳውቀው ። ምናልባት ስጦታ ልትሰጠው ሊሆን ይችላል ። ለምን እንደ ቀጠርከው ካላወቀ ግን የሞት ያህል ያስጨንቀዋል ። ስትቀጥረውም አንተም እርሱም የማትረበሹበት ቦታ ይሁን ። ያ ወዳጅህ የማይፈልገው ሰው ካለ ይዘህበት አትሂድ ። የማይፈልገውና ከዚህ በፊት ተነጋግራችሁበት የተዘጋ ነገርን አታንሣበት ። የቀጠሮውን ርእስ ለመንገር የማይቻል ከሆነ በሻይ ቡና ርእስ አግኘው ። እየጋበዝህ ግን ነገር አታብላው ። በምድር ላይ እጅግ ባለጌ የሆኑ ሰዎች ምግብ እየጋበዙ ነገር አብረው የሚያበሉ ናቸው ። አንድ ኪሎ ሥጋ ጋብዘው አራት ኪሎ ሚጥሚጣ ነስንሰው ይሄዳሉ ።
ቀጠሮ ስትሰጥ ያ ሰው ተጨንቆ እንደሆነ ለማረጋገጥ “ይመችሃል ወይ?” ብለህ ጠይቅ ። ምቾቱን ፍላጎቱን የምትነካበት ሰው እየጠላህ ይመጣል ። ሰው ከምንም በላይ ነጻነቱን የሚወድድ ፍጡር ነው ። ቀጠሮ እጅግ አድርገህ አክብር ። ቀጠሮህን እንዳትረሳ የሚያስታውሱ ማስታወሻዎች አድርግ ። በጸሎት ስፍራህ ወይም በቢሮህ ጠረጴዛ ላይ የቀጠሮህን ወረቀት አስቀምጥ ። ሊያነቃህ የሚችል ደወል ሙላ ። ሴቶች በማስታወስ ጎበዝ ናቸውና አስታውሱኝ ብለህ ንገራቸው ። ቀጠሮ ማክበር የመንፈሳዊነትም የሥልጣኔም መለኪያ ነው ። ምናልባት ያ ሰው ቢያረፍድ ደግሞም ቢቀር ጊዜህን እንዳታባክን የምትሠራውን ሥራ ፣ የምታነበውን መጽሐፍ ይዘህ ውጣ ። ቀረ ብለህ አትቀየም ። ለሰውም አትናገር ። ምናልባት በአደጋ ተሰናክሎ ይሆናል ። ወደ ቀጠሮህ ስትሄድ ጸልይ ። ንግግር ከመጀመራችሁ በፊትም ከዳኅፀ ልሳንና ልቡና እንዲሰውርህ አምላክህን ለምን ። በይበልጥ ለመጨዋወት ቀጠሮ መያዝ መልካም ነው ። አንዳንድ ጉዳዮች በስልክም ሊያልቁ ይችላሉና ለሁሉም ነገር ቀጠሮ ይያዝልኝ አትበል ። ዶሮ በጋን እንዳይሆንብህ ።
ሰው እፈልግሃለሁ ሲልህም አትኩሮት ስጥ ። ምናልባት ላለመኖር እየወሰነ ይሆናል ። ያንተ ቀጠሮ የሰውን ዕድሜ ማስቀጠል ከቻለ ከዚህ በላይ የምትኖርበት ዓላማ የለም ። ዛሬ ቢሞት ለመቅበር ይመችሃል ፣ ተጨንቄአለሁ ሲልህ አይመቸኝም አትበለው ። ያለችው ቀን ይህች ብቻ ልትሆን ትችላለች ። ብቻ ቀጠሮ አክብር ። ክቡርነትህን ማሳያ ነው ። ወላጆችህ ቀጠሮ ይከብዳቸው ነበር ። ሌሊቱን ሙሉ ሳይተኙ ሲንቆራጠጡ ያድሩ ነበር ። የሰውን ዋጋ ስላወቁ ዕድሜ ተሰጣቸው ። ለሰው ክብር የሌለው ዘመኑ አጭር ነው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም.
14. ቀጠሮ አክብር
ቀጠሮ የተጀመረው በእግዚአብሔር ነው ። ይህ ዓለም በመለኮታዊ ቀጠሮ የተፈጠረ ዓለም ነው ። ዘመን የሌለው ጌታ ዘመንን ለሰዎች ሰጠ ። ሰው በበደል በወደቀ ጊዜ ለመዳን ቀጠሮ ተሰጠው ። ሰው ከእግዚአብሔር ሳይለይ ከእግዚአብሔር ተለየ ። ለሆዱ እንጀራን ፣ ለአፍንጫው እስትንፋስን የሚያገኘው ከእግዚአብሔር ነው ። እንኳን በምድር በሲኦልም የሚኖረው በእግዚአብሔር ሕይወት ነው ። ጌታችን ወደ ምድር የመጣው ለሰዎች እንጀራ ለመስጠት ሳይሆን ራሱ ኅብስተ ሕይወት መሆኑን ለመግለጥ ነው ። 5500 ዘመን ሰው እንጀራ እየበላ ነበር ። ነፍሱ ግን ስደተኛና ረሀብተኛ ነበረች ። ሰው እግዚአብሔርን የሚክደው ከእግዚአብሔር የተቀበለውን እስትንፋስ መልሶ ሳይሆን በእግዚአብሔር ሕይወት ላይ ቆሞ ነው ። “በማን ላይ ቆመሽ ማንን ታሚያለሽ!” ይባላል ። እርሱ የካዱትን ቢክድ ኖሮ ፍጥረት በምድር ላይ ባልቆየ ነበር ። እግዚአብሔር ቀጠሮን መጀመሩ ብቻ ሳይሆን የሺህ ዘመናት ቀጠሮን የሚሰጥ አምላክ ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ ከሚኖረው ዕድሜ የረዘመ ቀጠሮ ተሰጠው ። ይህ ብዙ ፍቺ አለው ። የመጀመሪያው የሰው የህልውናው መጨረሻ መቃብር አይደለም ። በሥጋው ያጣውን በነፍሱ ሊክሰው የሚችል አምላክ አለው ። ዛሬ በሥጋ ጉድለታችን ስንፈራ ስንጨነቅ ጌታ ግን አይጨነቅም ። ምክንያቱም በሰማይም ሊጋብዘን ይችላልና።
እኛ ምንም ሳናደርግላቸው የሄዱት ወገኖቻችን የእግር እሳት ሆነውብን ይሆናል ። ደግነታችንን መቃብር ገድቦት ይሆናል ። በሰማያዊው ዓለምም የሚሰጥ አምላክ ግን ሞት ገደቡ አይደለም ። ከሰው ዕድሜ የሚረዝመው ቀጠሮ ለምን ተሰጠ ካልን ከ5500 ዘመን በኋላም የሚኖረው ሰው አዳም ስለሆነ ነው ። ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ ያላቸው እስከ ዓለም ፍጻሜ የሚኖሩ ሆነው አይደለም ። የእነርሱን ሥራ የሚያስቀጥል ሁሉ ሐዋርያ ስለሆነ በደቀ መዛሙርቶቻችሁ ላይ አድሬ እሠራለሁ ማለቱ ነው ። ስለዚህ ጴጥሮስ ይህን ሲሰማ ብሞትም ሕያው ነኝ ፤ የመንፈስ ልጅ አለኝ ብሎ ይጽናናል ። የአዳምን ቀጠሮ ክርስቶስ ሲሰቀል የነበሩ ሁሉ ፍጻሜውን አይተዋል ። አንድ አዳም ነን ። አንድ ስለሆንን የአዳም በደሉና ጥፋቱ አግኝቶናል ። የአዳም መዳኑና ካሣው ነጻ አውጥቶናል ። በሞት አንድ ሁነን በኑሮ መለያየታችንና መከፋፋታችን ይገርማል ።
የእግዚአብሔርን ቀጠሮ ልዩ የሚያደርገው የማይረሳ አምላክ መሆኑ ነው ። እኛ ቀጠሮአችንን በመርሳት ፣ ባለመመቸት ፣ ባለመፈለግ ፣ በመስጋት ፣ ሌላውን ጉዳይ በማስበለጥ እንሰርዛለን ። እግዚአብሔር ግን መርሳት የሌለበት የሕሊናት ሁሉ ባለቤት ነው ። አይመቸውም አይባልም ፣ እርሱ የሌለውን ና ብሎ መጥራት የሚችል አምላክ ነው ። በሰጠው ተስፋ አይጸጸትምና አልፈልጋችሁም አይለንም ። የሚሽረው የለምና አይሰጋም ። የዘላለም ጉዳዩ እኛ ነንና የእርሱ ውዶች ነን ። እግዚአብሔር ቀጠሮን የሚያከብር አምላክ ነው ። የእርሱ ተከታዮች እርሱን ይመስላሉና ቀጠሮን ያከብራሉ ። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤” ገላ 4፡4 ።
አንተም ቀጠሮ መስጠትን ልመድ ። ምክንያቱም አንተ እንደ ተመቸህ ያ ሰው አይመቸውምና በድንገት ውረድ ፍረድ አትበል ። ዓመት ሙሉ የረሳኸውን ሰው ዛሬ ስታገኘው አልላቀቅህም ብለህ ስሜታዊ አትሁን ። ቀጠሮ መስጠት ለሰውዬው ምቾት ፣ ለጉዳዩ ክብደት ነው ። ቀጠሮ በሰጠህ ጊዜ ወዳጅህ ተኝቶ እንዲያድር ወይም ተዘጋጅቶ እንዲመጣ ርእሱን ንገረው ። የምፈልግህ በዚህ ምክንያት ነው ብለህ አሳውቀው ። ምናልባት ስጦታ ልትሰጠው ሊሆን ይችላል ። ለምን እንደ ቀጠርከው ካላወቀ ግን የሞት ያህል ያስጨንቀዋል ። ስትቀጥረውም አንተም እርሱም የማትረበሹበት ቦታ ይሁን ። ያ ወዳጅህ የማይፈልገው ሰው ካለ ይዘህበት አትሂድ ። የማይፈልገውና ከዚህ በፊት ተነጋግራችሁበት የተዘጋ ነገርን አታንሣበት ። የቀጠሮውን ርእስ ለመንገር የማይቻል ከሆነ በሻይ ቡና ርእስ አግኘው ። እየጋበዝህ ግን ነገር አታብላው ። በምድር ላይ እጅግ ባለጌ የሆኑ ሰዎች ምግብ እየጋበዙ ነገር አብረው የሚያበሉ ናቸው ። አንድ ኪሎ ሥጋ ጋብዘው አራት ኪሎ ሚጥሚጣ ነስንሰው ይሄዳሉ ።
ቀጠሮ ስትሰጥ ያ ሰው ተጨንቆ እንደሆነ ለማረጋገጥ “ይመችሃል ወይ?” ብለህ ጠይቅ ። ምቾቱን ፍላጎቱን የምትነካበት ሰው እየጠላህ ይመጣል ። ሰው ከምንም በላይ ነጻነቱን የሚወድድ ፍጡር ነው ። ቀጠሮ እጅግ አድርገህ አክብር ። ቀጠሮህን እንዳትረሳ የሚያስታውሱ ማስታወሻዎች አድርግ ። በጸሎት ስፍራህ ወይም በቢሮህ ጠረጴዛ ላይ የቀጠሮህን ወረቀት አስቀምጥ ። ሊያነቃህ የሚችል ደወል ሙላ ። ሴቶች በማስታወስ ጎበዝ ናቸውና አስታውሱኝ ብለህ ንገራቸው ። ቀጠሮ ማክበር የመንፈሳዊነትም የሥልጣኔም መለኪያ ነው ። ምናልባት ያ ሰው ቢያረፍድ ደግሞም ቢቀር ጊዜህን እንዳታባክን የምትሠራውን ሥራ ፣ የምታነበውን መጽሐፍ ይዘህ ውጣ ። ቀረ ብለህ አትቀየም ። ለሰውም አትናገር ። ምናልባት በአደጋ ተሰናክሎ ይሆናል ። ወደ ቀጠሮህ ስትሄድ ጸልይ ። ንግግር ከመጀመራችሁ በፊትም ከዳኅፀ ልሳንና ልቡና እንዲሰውርህ አምላክህን ለምን ። በይበልጥ ለመጨዋወት ቀጠሮ መያዝ መልካም ነው ። አንዳንድ ጉዳዮች በስልክም ሊያልቁ ይችላሉና ለሁሉም ነገር ቀጠሮ ይያዝልኝ አትበል ። ዶሮ በጋን እንዳይሆንብህ ።
ሰው እፈልግሃለሁ ሲልህም አትኩሮት ስጥ ። ምናልባት ላለመኖር እየወሰነ ይሆናል ። ያንተ ቀጠሮ የሰውን ዕድሜ ማስቀጠል ከቻለ ከዚህ በላይ የምትኖርበት ዓላማ የለም ። ዛሬ ቢሞት ለመቅበር ይመችሃል ፣ ተጨንቄአለሁ ሲልህ አይመቸኝም አትበለው ። ያለችው ቀን ይህች ብቻ ልትሆን ትችላለች ። ብቻ ቀጠሮ አክብር ። ክቡርነትህን ማሳያ ነው ። ወላጆችህ ቀጠሮ ይከብዳቸው ነበር ። ሌሊቱን ሙሉ ሳይተኙ ሲንቆራጠጡ ያድሩ ነበር ። የሰውን ዋጋ ስላወቁ ዕድሜ ተሰጣቸው ። ለሰው ክብር የሌለው ዘመኑ አጭር ነው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (29)
ቀጠሮ ያለማክበር ችግር
በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ዓይነት ቀጠሮዎች አሉ ። ከወዳጅ ጋር ያለ ቀጠሮ አለ ። በዚህ ቀጠሮ ውስጥ ታማኝ አለመሆን ወዳጅን ሊያሳጣ ይችላል ። ወዳጅን ማጣት በፍቅር ረሀብ መቀጣት ነው ። በቤተ ክርስቲያን ውግዘት የሚባለው ተመክሮ ተዘክሮ እንቢ አልመለስም ያለውን ሰው መለየትና ፍቅር በማጣት እንዲቀጣ ማድረግ ነው ። ፍቅርን ማጣት ወይም ወዳጅን ማሳዘን ራስን እንደ ማውገዝ ነው ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ አለ ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ የሚያስጠይቅ ፣ በምክንያት የማይቀርበት ነው ። ወደ ፍርድ ቤት በሄድን ጊዜ እንፈራለን ። አንድ ቀን እንደ እኛ ችሎት ፊት የሚቆም ምድራዊ ዳኛ እንዲህ ካስፈራን ሰማያዊው ዳኝነት ብርቱ ነውና ከግፍ መራቅ ይገባናል ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ በብዛት ይከበራል ። የሥራ ቀጠሮ አለ ። የሥራ ቀጠሮ አንድ ሠራተኛ የሚመዘንበት የመጀመሪያው መለኪያ ነው ። ለሥራ ቃለ መጠይቅ ቀጠሮ አርፍዶ የሚመጣ ራሱን በራሱ ከዚያ ዕድል ለይቷል ። በአንድ ቀን አቋሙ ቀጣይ ዘመኑን አውቀውታልና ሊቀጥሩት አይፈልጉም ።
ቀጠሮ ስንሰጥ የሰጠነው ቃላችንን ነው ። ቃል የእግዚአብሔር ስም ነው ። የወልድም የኩነት መጠሪያው ነው ። ቃል ብርቱ ነገር ነው ። ቀጠሮ ከመሐላና ከጥብቅ አንቀጽ ጋር የሚወዳደር ነው ። ቀጠሮዎች በተለያየ ምክንያት እንቅፋት ይገጥማቸዋል ። በዚህ ዘመን ላይ ያሉ ወጣቶች የሁሉም ነገር ሥርና ቅርንጫፍ ገንዘብ እየመሰላቸው ይሳሳታሉ ። ወዳጅንም በገንዘብ እንደሚያመጡት ያስባሉ ። በገንዘብ የሚያስቅ ሰው ይገኝ ይሆናል ፣ የሚያስደስት ወዳጅ ግን አይገኝም ። በገንዘብ የሚከብብ ሰው ማግኘት ይቻላል ፣ ውስጥ የሚገባ የልብ ወዳጅ ግን አይገኝም ። ቀጠሮዎች ከሚሰረዙበት ምክንያት አንዱ ገንዘብን ማስበለጥ ወይም ምን አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ሊሆን ይችላል ። ፍቅር ግን ምን እሰጣለሁ እንጂ ምን አገኛለሁ ብሎ የሚያሰላ አይደለም ። ደስታ ያለው በመቀበል ሳይሆን በመስጠት ውስጥ ነው ። መርሳት የቀጠሮ እንቅፋት ነው ። መርሳት በዝንጉነት ጠባይ ፣ ብዙ አጀንዳና ወዳጅ በማብዛት ፣ ነሆለል ሰው በመሆን ፣ ሌላ ጊዜም በበሽታ የተነሣ የሚከሰት ነው ። መርሳትን ግን በጽሑፍና በደወል ማሸነፍ ይቻላል ። እየመረጥን የምንረሳ ከሆነም የእኛ ችግር ነው ። መርሳት ብዙ ጭንቀትና ውጥረት በማብዛት የሚመጣ በመሆኑ እኔ እኮ እረሳለሁ ብሎ የሚታለፍ አይደለም ። ያለ ዕድሜ የሆነ እንደሆነ ምንድነው ችግሬ ብሎ መጠየቅና መልሱን መፈለግ ያሻል ። አለማንበብ የመርሳትን ችግር ያመጣል ። ከሰዎች ጋር አለመገናኘትና አለማውራት መርሳትን ይወልዳል ።
ወዳጅን ቀጥሮ ማናገር ራስን የማከምና የመፈወስ ትልቅ ዘዴ ነው ። ብዙ ውጥረቶች ይቀላሉ ። የመኖር ፍላጎት እየጨመረ ይመጣል ። ያለንን ነገር በደስታ መጠቀም ይቻላል ። ተቀጣጥሮ ስልክ መዝጋት ይህ የጠባይ ዝቅታ ውጤት ነው ። ይህን የሚያደርጉ አገልጋይ ነን የሚሉም አሉ ። እንዲህ የኮሩበት አገልግሎት አንድ ቀን እየፈለጉም አያገኙትም ። አገልግሎትም ጡር አለው ። ሁልጊዜ ሊመቸን አይችልምና አስቀድመን ማሳወቅ ይገባናል ። ሰውን ከሰው አወዳድረን መቅረት ግን ነውር ነው ። የሁሉም ሰው ክብሩ እግዚአብሔር ነው ። ስለዚህ ሰው ሁሉ እኩል ነው ። አስድመን የሰጠነውን ቀጠሮ ማክበር ይገባል ። አንዳንድ ሰዎችን ተቀይመናቸዋል ወይም እነርሱን ማግኘት እየጎዳን ተቸግረን ይሆናል ። ይህንን በግልጥ ነግረን ማረም ወይም ቀጠሮ አለመያዝ ተገቢ ነው ። ሰው ለሰላሙ ዋጋ መክፈል አለበት ። ሰላማችንን ሠውተን የምናደርገው ግንኙነት ውስጣችንን እየጨረሰው ይመጣል ። ደግሞም የሚያኖረን እግዚአብሔር ነውና የሚያውኩንን የተቀየምናቸውን ሰዎች በግልጽ መንገርና መፍታት አስፈላጊ ነው ።
ቀጠሮአችንን ለማሳካት አለመቻላችንን መንገር ክብረት ነው ። እንዲሁ መቅረት ግን ያ ሰው ለእኛ ያለውን አመለካከት ዝቅ እንዲያደርግ ያስገድደዋል ። በመጀመሪያ ይበሳጭብናል ፣ ቀጥሎ ለእኛ ያሰበውን ትልልቅ ነገሮች መሰረዝ ይጀምራል ። ማንም ሰው ዋጋ የሚከፍለው ለአክባሪው ነው ። ሰዎች ቀጥረውን ቢቀሩ አንዳንድ ጊዜ ለበጎ ሊሆን ይችላል ። ሰብቅ ይዘውብን እየመጡ ከሆነ ለቀጣይ አንድ ዓመት ሰላማችንን ሊሰርቁት ነውና ቢቀሩ ይሻላል ። ወረኞችን አሉህና አሉሽ ማለት የሚወዱትን አለመቅጠርና አለማግኘት መልካም ነው ። ወሬውን እስኪነግሩን እንቅልፍ የላቸውም ፣ እኛ ሰምተን እንቅልፍ ስናጣ ግን ያን ጊዜ ይተኛሉ ። አምልኮተ እግዚአብሔርና ቃለ እግዚአብሔር በምንሰማበት ሰዓት ቀጠሮ መያዝ ክልክል ነው ። ካልሞትን በቀር ቤተ ክርስቲያን መቅረት የለብንም ። ስንሞትም የምንቀበረው እዚያው ነው ። በቀጠሮአችን ሰዓት ወዳጅነታችን እንዲቀጥል የማንስማማባቸውን ርእሶች መተው ይገባናል ። ክርክር አንዳንድ ጊዜ እኔ የበላይ ልሁን የሚያሰኝ የሥጋ ሥራ ነውና ፍቅርን ይጎዳል ። ቀጠሮን የሚጎዳው ሌላው ነገር ማርፈድ ነው ። አንዳንድ ማርፈድ የመቅረት ያህል ነው ። የአበሻ ቀጠሮ የሚባል የለም ። ቀጠሮ ፣ ቀጠሮ ነው ። ማርፈድን መዘናጋት ፣ መተኛት ፣ ጊዜን መለካት አለመቻል ፣ ወቅቱን አለማገናዘብ የሚወልደው ነው ። ማርፈድ ተጨማሪ ወጪ ነው ። አርፍደው አውሮፕላን ያመለጣቸው ተጨማሪ ወጪ ያወጣሉ ። ጓደኛቸው ተበሳጭቶባቸው የሄደባቸው ተጨማሪ ይቅርታና ማሳመን ያስፈልጋቸዋል ። ማርፈድ ጠባዩ ነው መባል ሞት ነው ። ሙሽሮች በሰዓቱ መድረስ የጠሩትን ሰው ማክበር ነው ። እስከማውቀው ድረስ ምግብ እያዩ ሙሽራን መጠበቅ የአገራችን ባሕል አይደለም ። እየበሉ እየጠጡ መጠበቅ ተገቢ ነው ። በሰርጉ ቀን ያረፈደ ፣ ትዳሩም ላይ ብዙ ማርፈድ ይገጥመዋል ።
ሰውን ማክበር ለራሳችን ያለን ክብር ውጤት ነው ። ቀጠሮ ማክበር ራስን ማክበር ነው ። ያደጉ አገሮች ሁሉ ያደጉት ቀጠሮን ወይም ሰዓትን በማክበር ነው ። ሰዓት ዋጋ ያጣው እኛ አገር ነው ። ማደግ ፈልገን በሰዓት ቀልደን አይሆንም ። ባለጉዳይ የቀደመው ሠራተኛ ማፈር አለበት ። አገር በዘፈን ሳይሆን በመሥዋዕትነት ታድጋለች ። ሌላ አገር ያለን ይመስል አንዷን አገራችንን ማጎሳቆል ሊበቃ ይገባዋል ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም.
ቀጠሮ ያለማክበር ችግር
በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ዓይነት ቀጠሮዎች አሉ ። ከወዳጅ ጋር ያለ ቀጠሮ አለ ። በዚህ ቀጠሮ ውስጥ ታማኝ አለመሆን ወዳጅን ሊያሳጣ ይችላል ። ወዳጅን ማጣት በፍቅር ረሀብ መቀጣት ነው ። በቤተ ክርስቲያን ውግዘት የሚባለው ተመክሮ ተዘክሮ እንቢ አልመለስም ያለውን ሰው መለየትና ፍቅር በማጣት እንዲቀጣ ማድረግ ነው ። ፍቅርን ማጣት ወይም ወዳጅን ማሳዘን ራስን እንደ ማውገዝ ነው ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ አለ ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ የሚያስጠይቅ ፣ በምክንያት የማይቀርበት ነው ። ወደ ፍርድ ቤት በሄድን ጊዜ እንፈራለን ። አንድ ቀን እንደ እኛ ችሎት ፊት የሚቆም ምድራዊ ዳኛ እንዲህ ካስፈራን ሰማያዊው ዳኝነት ብርቱ ነውና ከግፍ መራቅ ይገባናል ። የፍርድ ቤት ቀጠሮ በብዛት ይከበራል ። የሥራ ቀጠሮ አለ ። የሥራ ቀጠሮ አንድ ሠራተኛ የሚመዘንበት የመጀመሪያው መለኪያ ነው ። ለሥራ ቃለ መጠይቅ ቀጠሮ አርፍዶ የሚመጣ ራሱን በራሱ ከዚያ ዕድል ለይቷል ። በአንድ ቀን አቋሙ ቀጣይ ዘመኑን አውቀውታልና ሊቀጥሩት አይፈልጉም ።
ቀጠሮ ስንሰጥ የሰጠነው ቃላችንን ነው ። ቃል የእግዚአብሔር ስም ነው ። የወልድም የኩነት መጠሪያው ነው ። ቃል ብርቱ ነገር ነው ። ቀጠሮ ከመሐላና ከጥብቅ አንቀጽ ጋር የሚወዳደር ነው ። ቀጠሮዎች በተለያየ ምክንያት እንቅፋት ይገጥማቸዋል ። በዚህ ዘመን ላይ ያሉ ወጣቶች የሁሉም ነገር ሥርና ቅርንጫፍ ገንዘብ እየመሰላቸው ይሳሳታሉ ። ወዳጅንም በገንዘብ እንደሚያመጡት ያስባሉ ። በገንዘብ የሚያስቅ ሰው ይገኝ ይሆናል ፣ የሚያስደስት ወዳጅ ግን አይገኝም ። በገንዘብ የሚከብብ ሰው ማግኘት ይቻላል ፣ ውስጥ የሚገባ የልብ ወዳጅ ግን አይገኝም ። ቀጠሮዎች ከሚሰረዙበት ምክንያት አንዱ ገንዘብን ማስበለጥ ወይም ምን አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ሊሆን ይችላል ። ፍቅር ግን ምን እሰጣለሁ እንጂ ምን አገኛለሁ ብሎ የሚያሰላ አይደለም ። ደስታ ያለው በመቀበል ሳይሆን በመስጠት ውስጥ ነው ። መርሳት የቀጠሮ እንቅፋት ነው ። መርሳት በዝንጉነት ጠባይ ፣ ብዙ አጀንዳና ወዳጅ በማብዛት ፣ ነሆለል ሰው በመሆን ፣ ሌላ ጊዜም በበሽታ የተነሣ የሚከሰት ነው ። መርሳትን ግን በጽሑፍና በደወል ማሸነፍ ይቻላል ። እየመረጥን የምንረሳ ከሆነም የእኛ ችግር ነው ። መርሳት ብዙ ጭንቀትና ውጥረት በማብዛት የሚመጣ በመሆኑ እኔ እኮ እረሳለሁ ብሎ የሚታለፍ አይደለም ። ያለ ዕድሜ የሆነ እንደሆነ ምንድነው ችግሬ ብሎ መጠየቅና መልሱን መፈለግ ያሻል ። አለማንበብ የመርሳትን ችግር ያመጣል ። ከሰዎች ጋር አለመገናኘትና አለማውራት መርሳትን ይወልዳል ።
ወዳጅን ቀጥሮ ማናገር ራስን የማከምና የመፈወስ ትልቅ ዘዴ ነው ። ብዙ ውጥረቶች ይቀላሉ ። የመኖር ፍላጎት እየጨመረ ይመጣል ። ያለንን ነገር በደስታ መጠቀም ይቻላል ። ተቀጣጥሮ ስልክ መዝጋት ይህ የጠባይ ዝቅታ ውጤት ነው ። ይህን የሚያደርጉ አገልጋይ ነን የሚሉም አሉ ። እንዲህ የኮሩበት አገልግሎት አንድ ቀን እየፈለጉም አያገኙትም ። አገልግሎትም ጡር አለው ። ሁልጊዜ ሊመቸን አይችልምና አስቀድመን ማሳወቅ ይገባናል ። ሰውን ከሰው አወዳድረን መቅረት ግን ነውር ነው ። የሁሉም ሰው ክብሩ እግዚአብሔር ነው ። ስለዚህ ሰው ሁሉ እኩል ነው ። አስድመን የሰጠነውን ቀጠሮ ማክበር ይገባል ። አንዳንድ ሰዎችን ተቀይመናቸዋል ወይም እነርሱን ማግኘት እየጎዳን ተቸግረን ይሆናል ። ይህንን በግልጥ ነግረን ማረም ወይም ቀጠሮ አለመያዝ ተገቢ ነው ። ሰው ለሰላሙ ዋጋ መክፈል አለበት ። ሰላማችንን ሠውተን የምናደርገው ግንኙነት ውስጣችንን እየጨረሰው ይመጣል ። ደግሞም የሚያኖረን እግዚአብሔር ነውና የሚያውኩንን የተቀየምናቸውን ሰዎች በግልጽ መንገርና መፍታት አስፈላጊ ነው ።
ቀጠሮአችንን ለማሳካት አለመቻላችንን መንገር ክብረት ነው ። እንዲሁ መቅረት ግን ያ ሰው ለእኛ ያለውን አመለካከት ዝቅ እንዲያደርግ ያስገድደዋል ። በመጀመሪያ ይበሳጭብናል ፣ ቀጥሎ ለእኛ ያሰበውን ትልልቅ ነገሮች መሰረዝ ይጀምራል ። ማንም ሰው ዋጋ የሚከፍለው ለአክባሪው ነው ። ሰዎች ቀጥረውን ቢቀሩ አንዳንድ ጊዜ ለበጎ ሊሆን ይችላል ። ሰብቅ ይዘውብን እየመጡ ከሆነ ለቀጣይ አንድ ዓመት ሰላማችንን ሊሰርቁት ነውና ቢቀሩ ይሻላል ። ወረኞችን አሉህና አሉሽ ማለት የሚወዱትን አለመቅጠርና አለማግኘት መልካም ነው ። ወሬውን እስኪነግሩን እንቅልፍ የላቸውም ፣ እኛ ሰምተን እንቅልፍ ስናጣ ግን ያን ጊዜ ይተኛሉ ። አምልኮተ እግዚአብሔርና ቃለ እግዚአብሔር በምንሰማበት ሰዓት ቀጠሮ መያዝ ክልክል ነው ። ካልሞትን በቀር ቤተ ክርስቲያን መቅረት የለብንም ። ስንሞትም የምንቀበረው እዚያው ነው ። በቀጠሮአችን ሰዓት ወዳጅነታችን እንዲቀጥል የማንስማማባቸውን ርእሶች መተው ይገባናል ። ክርክር አንዳንድ ጊዜ እኔ የበላይ ልሁን የሚያሰኝ የሥጋ ሥራ ነውና ፍቅርን ይጎዳል ። ቀጠሮን የሚጎዳው ሌላው ነገር ማርፈድ ነው ። አንዳንድ ማርፈድ የመቅረት ያህል ነው ። የአበሻ ቀጠሮ የሚባል የለም ። ቀጠሮ ፣ ቀጠሮ ነው ። ማርፈድን መዘናጋት ፣ መተኛት ፣ ጊዜን መለካት አለመቻል ፣ ወቅቱን አለማገናዘብ የሚወልደው ነው ። ማርፈድ ተጨማሪ ወጪ ነው ። አርፍደው አውሮፕላን ያመለጣቸው ተጨማሪ ወጪ ያወጣሉ ። ጓደኛቸው ተበሳጭቶባቸው የሄደባቸው ተጨማሪ ይቅርታና ማሳመን ያስፈልጋቸዋል ። ማርፈድ ጠባዩ ነው መባል ሞት ነው ። ሙሽሮች በሰዓቱ መድረስ የጠሩትን ሰው ማክበር ነው ። እስከማውቀው ድረስ ምግብ እያዩ ሙሽራን መጠበቅ የአገራችን ባሕል አይደለም ። እየበሉ እየጠጡ መጠበቅ ተገቢ ነው ። በሰርጉ ቀን ያረፈደ ፣ ትዳሩም ላይ ብዙ ማርፈድ ይገጥመዋል ።
ሰውን ማክበር ለራሳችን ያለን ክብር ውጤት ነው ። ቀጠሮ ማክበር ራስን ማክበር ነው ። ያደጉ አገሮች ሁሉ ያደጉት ቀጠሮን ወይም ሰዓትን በማክበር ነው ። ሰዓት ዋጋ ያጣው እኛ አገር ነው ። ማደግ ፈልገን በሰዓት ቀልደን አይሆንም ። ባለጉዳይ የቀደመው ሠራተኛ ማፈር አለበት ። አገር በዘፈን ሳይሆን በመሥዋዕትነት ታድጋለች ። ሌላ አገር ያለን ይመስል አንዷን አገራችንን ማጎሳቆል ሊበቃ ይገባዋል ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (30)
15. የሰውን ነጻነት አክብር
አንዳንድ ገዥዎች ተነሥተው ነጻነት ሰጠናችሁ ይላሉ ። ሰው ለሰው ነጻነት መስጠት አይችልም ። የሰው ልጅ በተፈጥሮው ነጻነት ያለው ፍጡር ነው ። ደጋግ ነገሥታት ይህን ነጻነት ያከብሩ ፣ ያስመልሱ ይሆናል እንጂ ሊሰጡ አይችሉም ። የነጻነታችን ጌታ እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ነጻነት ነጻ መሆን እንደ ልብ መፋነን አይደለም ። ነጻነት የሥጋን ፣ የነፍስን ፣ የመንፈስን መንሰራፋት ማክበር ነው ። ሰው ወደ ወደደው አገርና ግዛት ሂዶ መኖር ፣ መንቀሳቀስና መነገድ ፣ ማተረፍና መውለድ ይችላል ። ይህ የሥጋ ነጻነት ነው ። የነፍስ ነጻነቱ የማሰብ ፣ የመናገርና የመኖር መብት ነው ። የመንፈስ ነጻነቱ የወደደውን አምላክ የማመን ፣ የማምለክና የመደሰት ልዕልና ነው ። ነገሥታት ይህን ነጻነት በበላይነት መጠበቅና ማስጠበቅ ይገባቸዋል ። እኔ እንደማስበው አስብ ማለት ሳይሆን ወደ እኛ አሳብ ሰዎችን በፍቅርና በአመክንዮ መሳብ እርሱ ነጻነትን ማክበር ነው ። እኛ እንደምናምነው የማያምን ሰውን ላጥፋህ ልደምስስህ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት ነው ። ይህች ዓለም የሰዎችም የእንስሳትም ዓለም ናት ። የጋራ ዓለም ናትና በጋራ ጉዳይ አንድ እየሆንን የሌላውን የግል መብት ማክበር አለብን ።
ስለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ብዙ ሰምተናል ፣ ብዙ ተናግረናል ። ዲሞክራሲ ባለመምጣቱም ኀዘን ገብቶናል ። የምንመኘውና ለዘመናት አትመጣም ወይ ብለን የምንጣራው ዲሞክራሲ የሌላውን መብት ማክበር ነው ። የራስን ግዴታ አውቆ የሌላውን ድንበር አለመዳፈር እርሱ ዲሞክራሲ ነው ። የሰዎችን የማመን ፣ የመናገርና የመኖር መብት ማክበር እርሱ ዲሞክራሲ ይባላል ። ዲሞክራሲ እንደ ምርት ከውጭ አገር ተጭኖ የሚመጣ አይደለም ። ዲሞክራሲ በመካከላችን ያለ ከራስ ወዳድነት ወጥተን ስለሌሎች በማሰብ ተግባራዊ የምናደርገው ነው ። ለራሳችንና ለወገናችን የነፈግነውን ዲሞክራሲ ማንም ሊሰጠን አይችልም ። ሁልጊዜ ተሸማቀን ከመኖር አንድ ጊዜ ተስማምተን ነጻነትን ማስፈን ይገባናል ። በኑሮአችን ውስጥ ሁሉም ሰው የራሱን ነጻነት ማስከበር ይፈልጋል ። ዲሞክራሲ ግን የሌላውን ነጻነት ማክበር ነው ። ዲሞክራሲን ለማስፈን ሰው ከራሱ ውጭ የሚታገለው ነገር የለም ። የነጻነታችን ትልቁ ጠላት እኛው ነን ።
ሰዎች የተለያየ ፖለቲካዊ አመለካከት ይኖራቸዋል ። እንደ እኔ አስቡ ብሎ መጫን ግን አትኑሩ ብሎ መፍረድ ነው ። እንጨትና እንጨት ሲፋተግ እሳት ይወጣዋል ። የሰዎችም መነጋገርና መከራከር እውቀትን ይፈነጥቃል ። አንድነት ማለት አንድ ዓይነት መሆን አይደለም ። የተለያየን መሆናችን ውበትን እንጂ ጭንቀትን የሚፈጥር አይደለም ። ሰዎች የራሳቸው ሃይማኖት አላቸው ። ከምናምነው ተቃራኒ ነገር ቢያምኑም የመኖር መብት አላቸው ። በምንም መንገድ አገር የዜጎች እንጂ የአንድ ሃይማኖት መሆን የለባትም ። ይህ የዜጎችን መከራ ያበዛል ። የነገሥታትም ድርሻ ሃይማኖትን ማስፋፋት ሳይሆን ሰላምና ዕድገትን ማስከበር ነው ። ሰዎች በመሰላቸው መንገድ ራሳቸውን በተለያየ ሱስ እየጎዱ ሊሆን ይችላል ። መጥላትና ማሳደድ ግን አንችልም ። ወደ ቀናው መንገድ በፍቅር መመለስ እንችላለን ። በምድር ላይ ለሃይማኖት ሰው የተሰጠው ትልቅ መሣሪያ ፍቅር ብቻ ነው ።
አንተ ግን የሌላውን ነጻነት አክብር ። ፍላጎታቸውን ተጭነህ ወዳጆችህ የምታደርጋቸው የሉም ። ለጊዜው ያደፍጡ ይሆናል ፣ አቅም ሲያገኙ ግን ጥለውህ ይሄዳሉ ። ሰዎች የራሳቸው የሆነ ጊዜ ሊፈልጉ ይችላሉ ። ለፍላጎታቸው ተዋቸው ። ዛሬ አንተን ማግኘት አይፈልጉ ይሆናል ። ከራሳቸው ችግር ጋር እየታገሉ እንጂ አንተ ርካሽ ሰው ስለሆንህ አይደለም ። ሁለት ጊዜ ያህል ደውለህ መልስ ካልሰጡህ ተዋቸው ። ስላልፈለጉህ በማትፈለግበት ቦታ ጊዜ አታጥፋ ። አንተን የሚፈልጉህ “በመጣልኝ” ብለው የሚሳሱልህ ብዙ አሉ ። ሰው የሚጠሉትን ሲያሳድድ ፣ የሚወዱትን ይከስራል ። ራስህን ዝቅ ማድረግ ተገቢ ነው ። ራስህን ርካሽ ማድረግ ግን እንድትጣል ያደርግሃል ። በመገኘትህ የምትጠቅማቸው ሰዎች ይኖራሉ ፣ መገኘትህንና ቅርበትህን ካቃለሉ ግን ራቃቸው ። ክብር በሌለበት ፍቅር የለም ፣ ፍቅር በሌለበትም እግዚአብሔር የለም ። ማንንም ሰው አሳምን እንጂ አትለማመጥ ። የሰውነት ክፍሎችህ ካንተ ጋር ናቸው ። በሰው እጅ አትጎርስም ፣ በሰው ትንፋሽ አትኖርም ። የራስህን ሕይወት የሰጠህን ጌታ አክብር ።
ሰዎች የሚወድዱት አለባበስ ፣ የኑሮ ዘይቤ ፣ የቤት አሠራር ፣ የትዳር ምሪት ፣ የልጆች አስተዳደግ አላቸው ። ቋሚውን እውነት አሳውቃቸው እንጂ በእኔ መንገድ ካልሄዳችሁ እያልህ አትጎትታቸው ። የጣሉህ ሰዎች የጎተትካቸው እንቢተኞች ናቸው ። እገሌ ይጾማል አይጾምም ፣ እገሌ በቅድስና ነው ያለው በርኵሰት እያለህ በሰው ጓዳ አትዋል ። ይህ ርካሽነት ነው ። የራስህን ኑሮ ኑር ። ካንተ የሚፈልጉ ከሆነ እንኳን በወዳጆችህ በጠላትህም አትጨክን ። እንኳን አንተን ሰጪ አደረገህ ። የማይፈልጉ ሰዎችን ካልመከርኩ አትበል ። እርዳታህን የሚሸሹ ሰዎችን በግድ ካልረዳሁ አትበል ። የከበረውን ነገር ዋጋ በማይሰጡ ሰዎች ፊት አትጣል ። ውድ ጊዜህንም ተራ ነገርን ከሚፈልጉ ሰዎች ጋር አታባክን ። በማትፈለግበት ቦታ አትገኝ ። ምንም ነገር ስታደርግ ሰዎችን አስፈቅድ ። ያለ ፈቃዳቸው የምታደርገው ነገር ላንተም ለእነርሱም ደስታ አይሰጥም ። በጣም ጥንቃቄም ለስህተት ይዳርጋልና እጅግም ጠንቃቃ ፣ እጅግም ጻድቅ አትሁን ። ወደ ጓደኛህ ቤት እግር አታብዛ ። ወዳንተ ቤት እግር ቢያበዙ ግን ክርስቶስን እንደምትቀበል አድርገህ ተቀበላቸው ። የልብህን ሁሉ ፣ ለሁሉ አትናገር ። ሰዎችም ሁሉን እንዲነግሩህ አትፈልግ ። ባለትዳሮች ካልጋበዙህ በቀር ልዳኛችሁ አትበል ። ባልዬው በሌለበት ቤት ሚስቲቱ ብትቀጥርህ አትሂድ ።
በአገራችን በሰው ገላም ካላዘዝን የምንል ደፋሮች ነን ። የምንኖረውም በመጠባበቅ እንጂ ያመንበትን አይደለም ። በገዛ ሕይወታችን ላይ ድራማ የምንሠራ ምስኪኖች ነን ። ማኅበራዊነታችን መልካም ነው ። የሌላውን መብት መጋፋት ግን ነውር ነው ። በሁሉም ነገር ላይ አስተያየት መስጠት ግዴታችን ይመስለናል ። ለሁሉም መልስ አይሰጥም ። ብቻ የሰዎችን ነጻነት አክብር። ሊሄዱ የሚፈልጉትን በሰላም ሸኝ ። የሚመጡትን ደጎች ተቀበል ። በትዝታ ታስረህ የዛሬን ኑሮ አትሰርዝ ። ጨርሻለሁ ብለው መሄድ የማያውቁ ሰዎችን አጨራረሱን አሳያቸው እንጂ እንዲያውኩህ አትፍቀድላቸው ። ምክንያቱም ያንተ ኑሮ ይህ ነው ፣ እነርሱ ግን አማራጭ አላቸውና ። ርቀውህ የነበሩ ሰዎች እንደገና ሲመጡ በጥንቃቄ ተቀበል ። ምናልባት ያልጨረሱትን ተንኮል ለመጨረስ ይሆናል ። መጠንቀቅ ይቅር አለማለት አይደለምና ። ዕድሜህ እንዳያጥር ለአልምጦች ጋር አትኑር ! ከራስህ ጋር መሆን ጣፋጭ ነው ፣ ሰዎች ካልመጡ ሕይወትህ የተሰረዘ አይምሰልህ ! ሁልጊዜ ሰዎች አይገኙምና ከራስህ ጋር ልታደርግ የሚገባውን ዛሬውኑ አቅድ ! የምትፈልገውን በትክክል እወቅ ፤ ሕይወትህ መደሰት ትጀምራለች!
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም.
15. የሰውን ነጻነት አክብር
አንዳንድ ገዥዎች ተነሥተው ነጻነት ሰጠናችሁ ይላሉ ። ሰው ለሰው ነጻነት መስጠት አይችልም ። የሰው ልጅ በተፈጥሮው ነጻነት ያለው ፍጡር ነው ። ደጋግ ነገሥታት ይህን ነጻነት ያከብሩ ፣ ያስመልሱ ይሆናል እንጂ ሊሰጡ አይችሉም ። የነጻነታችን ጌታ እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ነጻነት ነጻ መሆን እንደ ልብ መፋነን አይደለም ። ነጻነት የሥጋን ፣ የነፍስን ፣ የመንፈስን መንሰራፋት ማክበር ነው ። ሰው ወደ ወደደው አገርና ግዛት ሂዶ መኖር ፣ መንቀሳቀስና መነገድ ፣ ማተረፍና መውለድ ይችላል ። ይህ የሥጋ ነጻነት ነው ። የነፍስ ነጻነቱ የማሰብ ፣ የመናገርና የመኖር መብት ነው ። የመንፈስ ነጻነቱ የወደደውን አምላክ የማመን ፣ የማምለክና የመደሰት ልዕልና ነው ። ነገሥታት ይህን ነጻነት በበላይነት መጠበቅና ማስጠበቅ ይገባቸዋል ። እኔ እንደማስበው አስብ ማለት ሳይሆን ወደ እኛ አሳብ ሰዎችን በፍቅርና በአመክንዮ መሳብ እርሱ ነጻነትን ማክበር ነው ። እኛ እንደምናምነው የማያምን ሰውን ላጥፋህ ልደምስስህ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት ነው ። ይህች ዓለም የሰዎችም የእንስሳትም ዓለም ናት ። የጋራ ዓለም ናትና በጋራ ጉዳይ አንድ እየሆንን የሌላውን የግል መብት ማክበር አለብን ።
ስለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ብዙ ሰምተናል ፣ ብዙ ተናግረናል ። ዲሞክራሲ ባለመምጣቱም ኀዘን ገብቶናል ። የምንመኘውና ለዘመናት አትመጣም ወይ ብለን የምንጣራው ዲሞክራሲ የሌላውን መብት ማክበር ነው ። የራስን ግዴታ አውቆ የሌላውን ድንበር አለመዳፈር እርሱ ዲሞክራሲ ነው ። የሰዎችን የማመን ፣ የመናገርና የመኖር መብት ማክበር እርሱ ዲሞክራሲ ይባላል ። ዲሞክራሲ እንደ ምርት ከውጭ አገር ተጭኖ የሚመጣ አይደለም ። ዲሞክራሲ በመካከላችን ያለ ከራስ ወዳድነት ወጥተን ስለሌሎች በማሰብ ተግባራዊ የምናደርገው ነው ። ለራሳችንና ለወገናችን የነፈግነውን ዲሞክራሲ ማንም ሊሰጠን አይችልም ። ሁልጊዜ ተሸማቀን ከመኖር አንድ ጊዜ ተስማምተን ነጻነትን ማስፈን ይገባናል ። በኑሮአችን ውስጥ ሁሉም ሰው የራሱን ነጻነት ማስከበር ይፈልጋል ። ዲሞክራሲ ግን የሌላውን ነጻነት ማክበር ነው ። ዲሞክራሲን ለማስፈን ሰው ከራሱ ውጭ የሚታገለው ነገር የለም ። የነጻነታችን ትልቁ ጠላት እኛው ነን ።
ሰዎች የተለያየ ፖለቲካዊ አመለካከት ይኖራቸዋል ። እንደ እኔ አስቡ ብሎ መጫን ግን አትኑሩ ብሎ መፍረድ ነው ። እንጨትና እንጨት ሲፋተግ እሳት ይወጣዋል ። የሰዎችም መነጋገርና መከራከር እውቀትን ይፈነጥቃል ። አንድነት ማለት አንድ ዓይነት መሆን አይደለም ። የተለያየን መሆናችን ውበትን እንጂ ጭንቀትን የሚፈጥር አይደለም ። ሰዎች የራሳቸው ሃይማኖት አላቸው ። ከምናምነው ተቃራኒ ነገር ቢያምኑም የመኖር መብት አላቸው ። በምንም መንገድ አገር የዜጎች እንጂ የአንድ ሃይማኖት መሆን የለባትም ። ይህ የዜጎችን መከራ ያበዛል ። የነገሥታትም ድርሻ ሃይማኖትን ማስፋፋት ሳይሆን ሰላምና ዕድገትን ማስከበር ነው ። ሰዎች በመሰላቸው መንገድ ራሳቸውን በተለያየ ሱስ እየጎዱ ሊሆን ይችላል ። መጥላትና ማሳደድ ግን አንችልም ። ወደ ቀናው መንገድ በፍቅር መመለስ እንችላለን ። በምድር ላይ ለሃይማኖት ሰው የተሰጠው ትልቅ መሣሪያ ፍቅር ብቻ ነው ።
አንተ ግን የሌላውን ነጻነት አክብር ። ፍላጎታቸውን ተጭነህ ወዳጆችህ የምታደርጋቸው የሉም ። ለጊዜው ያደፍጡ ይሆናል ፣ አቅም ሲያገኙ ግን ጥለውህ ይሄዳሉ ። ሰዎች የራሳቸው የሆነ ጊዜ ሊፈልጉ ይችላሉ ። ለፍላጎታቸው ተዋቸው ። ዛሬ አንተን ማግኘት አይፈልጉ ይሆናል ። ከራሳቸው ችግር ጋር እየታገሉ እንጂ አንተ ርካሽ ሰው ስለሆንህ አይደለም ። ሁለት ጊዜ ያህል ደውለህ መልስ ካልሰጡህ ተዋቸው ። ስላልፈለጉህ በማትፈለግበት ቦታ ጊዜ አታጥፋ ። አንተን የሚፈልጉህ “በመጣልኝ” ብለው የሚሳሱልህ ብዙ አሉ ። ሰው የሚጠሉትን ሲያሳድድ ፣ የሚወዱትን ይከስራል ። ራስህን ዝቅ ማድረግ ተገቢ ነው ። ራስህን ርካሽ ማድረግ ግን እንድትጣል ያደርግሃል ። በመገኘትህ የምትጠቅማቸው ሰዎች ይኖራሉ ፣ መገኘትህንና ቅርበትህን ካቃለሉ ግን ራቃቸው ። ክብር በሌለበት ፍቅር የለም ፣ ፍቅር በሌለበትም እግዚአብሔር የለም ። ማንንም ሰው አሳምን እንጂ አትለማመጥ ። የሰውነት ክፍሎችህ ካንተ ጋር ናቸው ። በሰው እጅ አትጎርስም ፣ በሰው ትንፋሽ አትኖርም ። የራስህን ሕይወት የሰጠህን ጌታ አክብር ።
ሰዎች የሚወድዱት አለባበስ ፣ የኑሮ ዘይቤ ፣ የቤት አሠራር ፣ የትዳር ምሪት ፣ የልጆች አስተዳደግ አላቸው ። ቋሚውን እውነት አሳውቃቸው እንጂ በእኔ መንገድ ካልሄዳችሁ እያልህ አትጎትታቸው ። የጣሉህ ሰዎች የጎተትካቸው እንቢተኞች ናቸው ። እገሌ ይጾማል አይጾምም ፣ እገሌ በቅድስና ነው ያለው በርኵሰት እያለህ በሰው ጓዳ አትዋል ። ይህ ርካሽነት ነው ። የራስህን ኑሮ ኑር ። ካንተ የሚፈልጉ ከሆነ እንኳን በወዳጆችህ በጠላትህም አትጨክን ። እንኳን አንተን ሰጪ አደረገህ ። የማይፈልጉ ሰዎችን ካልመከርኩ አትበል ። እርዳታህን የሚሸሹ ሰዎችን በግድ ካልረዳሁ አትበል ። የከበረውን ነገር ዋጋ በማይሰጡ ሰዎች ፊት አትጣል ። ውድ ጊዜህንም ተራ ነገርን ከሚፈልጉ ሰዎች ጋር አታባክን ። በማትፈለግበት ቦታ አትገኝ ። ምንም ነገር ስታደርግ ሰዎችን አስፈቅድ ። ያለ ፈቃዳቸው የምታደርገው ነገር ላንተም ለእነርሱም ደስታ አይሰጥም ። በጣም ጥንቃቄም ለስህተት ይዳርጋልና እጅግም ጠንቃቃ ፣ እጅግም ጻድቅ አትሁን ። ወደ ጓደኛህ ቤት እግር አታብዛ ። ወዳንተ ቤት እግር ቢያበዙ ግን ክርስቶስን እንደምትቀበል አድርገህ ተቀበላቸው ። የልብህን ሁሉ ፣ ለሁሉ አትናገር ። ሰዎችም ሁሉን እንዲነግሩህ አትፈልግ ። ባለትዳሮች ካልጋበዙህ በቀር ልዳኛችሁ አትበል ። ባልዬው በሌለበት ቤት ሚስቲቱ ብትቀጥርህ አትሂድ ።
በአገራችን በሰው ገላም ካላዘዝን የምንል ደፋሮች ነን ። የምንኖረውም በመጠባበቅ እንጂ ያመንበትን አይደለም ። በገዛ ሕይወታችን ላይ ድራማ የምንሠራ ምስኪኖች ነን ። ማኅበራዊነታችን መልካም ነው ። የሌላውን መብት መጋፋት ግን ነውር ነው ። በሁሉም ነገር ላይ አስተያየት መስጠት ግዴታችን ይመስለናል ። ለሁሉም መልስ አይሰጥም ። ብቻ የሰዎችን ነጻነት አክብር። ሊሄዱ የሚፈልጉትን በሰላም ሸኝ ። የሚመጡትን ደጎች ተቀበል ። በትዝታ ታስረህ የዛሬን ኑሮ አትሰርዝ ። ጨርሻለሁ ብለው መሄድ የማያውቁ ሰዎችን አጨራረሱን አሳያቸው እንጂ እንዲያውኩህ አትፍቀድላቸው ። ምክንያቱም ያንተ ኑሮ ይህ ነው ፣ እነርሱ ግን አማራጭ አላቸውና ። ርቀውህ የነበሩ ሰዎች እንደገና ሲመጡ በጥንቃቄ ተቀበል ። ምናልባት ያልጨረሱትን ተንኮል ለመጨረስ ይሆናል ። መጠንቀቅ ይቅር አለማለት አይደለምና ። ዕድሜህ እንዳያጥር ለአልምጦች ጋር አትኑር ! ከራስህ ጋር መሆን ጣፋጭ ነው ፣ ሰዎች ካልመጡ ሕይወትህ የተሰረዘ አይምሰልህ ! ሁልጊዜ ሰዎች አይገኙምና ከራስህ ጋር ልታደርግ የሚገባውን ዛሬውኑ አቅድ ! የምትፈልገውን በትክክል እወቅ ፤ ሕይወትህ መደሰት ትጀምራለች!
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም.
የማርቆስ ወንጌል ትርጓሜ 21
ማር.4፥ 21 - 41
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
ማር.4፥ 21 - 41
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
እግዚአብሔር ይናገራል 3
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
በ#ዲያቆን #አሸናፊ #መኮንን የተዘጋጀ ስብከት
አሁን በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል ። ይከታተሉ
የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ትምህርቶችና ስብከቶች ለመከታተል ከሥር የተቀመጡትን ገጾች ይመልከቱ፡-
https://www.tg-me.com/Nolawi ኖላዊ/com.Nolawii
https://www.tg-me.com/nolawisebketoch
https://www.facebook.co m/ashenafi.mekonnen.357
https://youtu.be/3qfQp9yYmHY
www.ashenafimekonen.com
Telegram
Nolawi ኖላዊ
ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ!
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኮንን
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (31)
16. ዜማ
ዜማ በሰው ነፍስ ውስጥ የተቀመጠ ጥልቅ ፍላጎት ነው ። ዜማ ምድራዊውን ሰው ሰማያዊ የሚያደርግ ነው ። የነፍስ ሀልዎት መገለጫ ነው ። ነፍስ ስትታደስ ሥጋም አብሮ እንደሚታደስ ዜማ ይነግረናል ። ዜማ ሰዎችና እንስሳት የሚካፈሉት የጋራ ፍላጎት ነው ። ዜማ ሲሰሙ አደገኛ የሚባሉ አራዊት ይመሰጣሉ ። ዜማ ጨካኙን የማራራት አቅም አለው ። ቀሳውስት ቸገረኝ እንጂ ጨነቀኝ ሲሉ አይሰማም ። ጭንቀትም በጉልህ አይታይባቸውም ። የዚህ ምሥጢሩ ዜማ ነው ። ዜማ ያድሳል ። የከበደንን ደመና ያነሣል ። ዜማ ደስታን ፣ የአእምሮ መፍታታትን ፣ ጣዕምን ፣ ተደማጭነትን ፣ ተወዳጅነትን ያጎናጽፋል ። በዜማ ውስጥ ብዙ መልእክቶች አሉ ። ዜማ ምስጋናንና ትምህርትን በጣዕም ለማስተላለፍ የሚረዳ ነው ። ዜማ የታላቅ ፍልስፍና መገለጫ ነው ። ዜማ በሰማይ የሚጠብቀን ድግስ ነው ። ቅዱስ ያሬድ የዜማው ባላባት እስከ ዛሬ ድረስ ተሰምተው የማይጠገቡ ዜማዎችን ለቤተ ክርስቲያን አበርክቷል ። በርግጥ መንፈሳውያን እንደ መሆናችን እግዚአብሔር እንደ ገለጠለት እናምናለን ፤ የስጦታውን ምንጭም አንስትም ። ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ተቀብሮ መቅረቱ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ነው ። የሌላው ዓለም ሀብት ቢሆን ኖሮ የየቀኑ ርእስ ይሆን ነበር ።
ዜማ የትልቅ ሥልጣኔ መገለጫ ነው ። ዜማን በኖታ ዓለም ከማቅረቡ በፊት ቅዱስ ያሬድ አዘጋጅቶታል ። ዜማ ቋንቋ ነው ። ስብሐተ እግዚአብሔር የሚደርስበት ሰረገላ ነው ። ዜማ ክንፍ ነው ፣ ወደ ሰማየ ሰማያት የምንወጣበት ነው ። ጸሎታችንን በዜማ ብናደርስ የምንጸልየውን እናስተውለዋለን ፣ እንባ በዓይናችን ይሞላል ፣ ልባችን በመለኮት ፍቅር መቅለጥ ይጀምራል ። ጮክ ብለን ማዜምና መዘመር በጣም ወሳኝ ነው ። በሳምንት አንድ ቀን እንኳ አፍ አውጥተን ብናዜም የከበደን ነገር ይቀለናል ። ዜማ የነፍስ ምግብ ፣ የጭንቀት ዱላ ነው ። ማንጎራጎር የሚወድዱ ሰዎች ደስተኞች ናቸው ። እያንጎራጎሩ ሲያለቅሱ ይታደሳሉ ። እንባ ወደ ውጭ ካልፈሰሰ ወደ ውስጥ ይፈሳል ። ያን ጊዜ ሰባራ ሰው ያደርገናል ። ዜማ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚቀርብበት መሠዊያ ነው ። እግዚአብሔርን የሚማርከው ዜማው ሳይሆን የልባችን መቃጠል ነው ። ዜማ ግን ምድራዊነታችንን ሰማያዊ ያደርገዋል ።
የሚያዜሙ ሰዎች ብዙ ጊዜ እውቀት አይወድዱም ። በዚህ ምክንያት “ድምፅና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል” እየተባሉ ይተቻሉ ። የሚያዜም ሰው ግጥም ፣ ቅኔ ፣ የንግግር ችሎታን ማዳበር አለበት ። በርግጥ የሊቃውንቱን ቅኔ ለዓለም የሚያደርሱት ዜመኞች ናቸው ። የሚያዜሙም ከእውቀት መራቅ አይገባቸውም ። ዜማ ሙያ ሲሆን ለጥቂቶች ነው ። አምልኮ ሲሆን ግን ለሰው ልጆች ሁሉ ነው ። አእዋፋት በማለዳ ያዜማሉ ። ባናያቸውም እንወዳቸዋለን ፣ ዜማ እንደሚያነቃም እንረዳለን ። የሚያዜሙ ሰዎች በሰው ነፍስ ውስጥ አሉ ። ሰው ከውጫዊ አካሉ ይልቅ ነፍሱ ስፋት እንዳላት ዜማና ተጽእኖው ይገልጥልናል ። ዜማ የተለያየ መልእክት አለው ብለናል ። የማኅበረሰብ መግባቢያ ቋንቋ ነው ። ሰርግን ፣ ጦርነትን ፣ ደስታን ፣ ኀዘንን በዜማ እንወጣለን ። ሥርዓት ያላቸው ዜማዎች ፣ የማኅበረሰቡ ግኝት የሆኑ ግጥሞች ለሰርግ መዋል አለባቸው ። ዜማ የዝሙት ማስታወቂያ ሲሆንና እጅና እግርን ማወደሻ ሁኖ ሲቀር ይተቻል ። መንፈሳዊነት ማኅበረሰብን የሚደፈጥጥ አይደለም ። በሰርጌ ጌታ ይክበር የሚሉ አሉ ፣ ጥሩ ነው ። ጌታ ግን የሚከብረው በሁለት ሰዓት ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን በኑሮ ውስጥ ነው ። ሚስትህን በአጋፔ ፍቅር ስትወዳት ፣ ባልሽን እንደ ራስ ስታከብሪው ያን ጊዜ እግዚአብሔር ይከብራል ።
በዜማ መለቀስ ፣ ኀዘን መተንፈስ አለበት ። ያልወጡ ኀዘኖች ብዙዎችን ለድባቴ እየዳረጉ ይገኛሉ ። አገራችን ታላላቅ ሰዎች የነበሩባትና ያሉባት አገር ናትና ደስታንም ኀዘንንም መግለጫ አበጅተዋል ። ደግሞም የባሕላችን ማሳያ ነውና ሊከበር ይገባዋል ። አለማልቀስ ዘመናዊነትም መንፈሳዊነትም አይደለም ። ሬሳ አስቀምጦ አላለቅስም ማለት ጉራ ሲሆን አብረው የሚያላቅሱ ሲሄዱ ውጋቱ ይጀምራቸዋል ። እንዴት ሰው ሞትን እያስተናገደ ለማልቀስ ይሳሳል ?
አገርን የሚያወድሱ ፣ ጀግንነትን የሚያነሣሡ ዜማዎች አንድን ትውልድ የአገር ዘብ አድርጎ የማቆም አቅም አላቸው ። እዚህ የምንጽፈውና የምናመልከው በዳር ድንበር የሚጠብቅ ወታደር ስላለ መሆኑን ማወቅና ክብር መስጠት ይገባናል ። ከዜማ ጋር የዜማ መሣሪያዎችን መለማመድ ግድ ይላል ። ቢያንስ አንድ የዜማ መሣሪያ ማወቅ ለቀጣዩ ዕድሜ ፣ ለእርጅና ብቸኝነት ወሳኝ ነው ። ዜማ ለማኞች እንኳ ጨካኙን የሚያራሩበት ነው ። የዜማ ዕቃ ይዘው የሚያዜሙም ከመንገዳችን ቆም ያደርጉናል ። ዘወትር ከጸሎታችን ጋር ድምፅ አውጥተን ብንዘምር ላሉብን ውጥረቶች ቅለት ይሰጠናል ። ነገር ግን አጠገባችን ያለውን ሰው እንዳንረብሽ ፣ ተወዳጁን አምላክ በእኛ ረባሽነት እንዳናስጠላው መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። ዜማ የራሱ ሥርዓት አለውና ሊጠና ፣ ሊያድግና ሊበረታታ ይገባዋል ። ከሕይወት ሥነ ሥርዓት አንዱ ዜማ ማዜም ነው ። በቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት የዜማ ዕቃ ጸናጽል ፣ መቋሚያና ከበሮ ነው ። የምእመናን የዜማ ዕቃ በገና ፣ መሰንቆ ፣ ክራር ፣ እንዚራ ተጠቃሽ ናቸው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ.ም.
16. ዜማ
ዜማ በሰው ነፍስ ውስጥ የተቀመጠ ጥልቅ ፍላጎት ነው ። ዜማ ምድራዊውን ሰው ሰማያዊ የሚያደርግ ነው ። የነፍስ ሀልዎት መገለጫ ነው ። ነፍስ ስትታደስ ሥጋም አብሮ እንደሚታደስ ዜማ ይነግረናል ። ዜማ ሰዎችና እንስሳት የሚካፈሉት የጋራ ፍላጎት ነው ። ዜማ ሲሰሙ አደገኛ የሚባሉ አራዊት ይመሰጣሉ ። ዜማ ጨካኙን የማራራት አቅም አለው ። ቀሳውስት ቸገረኝ እንጂ ጨነቀኝ ሲሉ አይሰማም ። ጭንቀትም በጉልህ አይታይባቸውም ። የዚህ ምሥጢሩ ዜማ ነው ። ዜማ ያድሳል ። የከበደንን ደመና ያነሣል ። ዜማ ደስታን ፣ የአእምሮ መፍታታትን ፣ ጣዕምን ፣ ተደማጭነትን ፣ ተወዳጅነትን ያጎናጽፋል ። በዜማ ውስጥ ብዙ መልእክቶች አሉ ። ዜማ ምስጋናንና ትምህርትን በጣዕም ለማስተላለፍ የሚረዳ ነው ። ዜማ የታላቅ ፍልስፍና መገለጫ ነው ። ዜማ በሰማይ የሚጠብቀን ድግስ ነው ። ቅዱስ ያሬድ የዜማው ባላባት እስከ ዛሬ ድረስ ተሰምተው የማይጠገቡ ዜማዎችን ለቤተ ክርስቲያን አበርክቷል ። በርግጥ መንፈሳውያን እንደ መሆናችን እግዚአብሔር እንደ ገለጠለት እናምናለን ፤ የስጦታውን ምንጭም አንስትም ። ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ተቀብሮ መቅረቱ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ነው ። የሌላው ዓለም ሀብት ቢሆን ኖሮ የየቀኑ ርእስ ይሆን ነበር ።
ዜማ የትልቅ ሥልጣኔ መገለጫ ነው ። ዜማን በኖታ ዓለም ከማቅረቡ በፊት ቅዱስ ያሬድ አዘጋጅቶታል ። ዜማ ቋንቋ ነው ። ስብሐተ እግዚአብሔር የሚደርስበት ሰረገላ ነው ። ዜማ ክንፍ ነው ፣ ወደ ሰማየ ሰማያት የምንወጣበት ነው ። ጸሎታችንን በዜማ ብናደርስ የምንጸልየውን እናስተውለዋለን ፣ እንባ በዓይናችን ይሞላል ፣ ልባችን በመለኮት ፍቅር መቅለጥ ይጀምራል ። ጮክ ብለን ማዜምና መዘመር በጣም ወሳኝ ነው ። በሳምንት አንድ ቀን እንኳ አፍ አውጥተን ብናዜም የከበደን ነገር ይቀለናል ። ዜማ የነፍስ ምግብ ፣ የጭንቀት ዱላ ነው ። ማንጎራጎር የሚወድዱ ሰዎች ደስተኞች ናቸው ። እያንጎራጎሩ ሲያለቅሱ ይታደሳሉ ። እንባ ወደ ውጭ ካልፈሰሰ ወደ ውስጥ ይፈሳል ። ያን ጊዜ ሰባራ ሰው ያደርገናል ። ዜማ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚቀርብበት መሠዊያ ነው ። እግዚአብሔርን የሚማርከው ዜማው ሳይሆን የልባችን መቃጠል ነው ። ዜማ ግን ምድራዊነታችንን ሰማያዊ ያደርገዋል ።
የሚያዜሙ ሰዎች ብዙ ጊዜ እውቀት አይወድዱም ። በዚህ ምክንያት “ድምፅና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል” እየተባሉ ይተቻሉ ። የሚያዜም ሰው ግጥም ፣ ቅኔ ፣ የንግግር ችሎታን ማዳበር አለበት ። በርግጥ የሊቃውንቱን ቅኔ ለዓለም የሚያደርሱት ዜመኞች ናቸው ። የሚያዜሙም ከእውቀት መራቅ አይገባቸውም ። ዜማ ሙያ ሲሆን ለጥቂቶች ነው ። አምልኮ ሲሆን ግን ለሰው ልጆች ሁሉ ነው ። አእዋፋት በማለዳ ያዜማሉ ። ባናያቸውም እንወዳቸዋለን ፣ ዜማ እንደሚያነቃም እንረዳለን ። የሚያዜሙ ሰዎች በሰው ነፍስ ውስጥ አሉ ። ሰው ከውጫዊ አካሉ ይልቅ ነፍሱ ስፋት እንዳላት ዜማና ተጽእኖው ይገልጥልናል ። ዜማ የተለያየ መልእክት አለው ብለናል ። የማኅበረሰብ መግባቢያ ቋንቋ ነው ። ሰርግን ፣ ጦርነትን ፣ ደስታን ፣ ኀዘንን በዜማ እንወጣለን ። ሥርዓት ያላቸው ዜማዎች ፣ የማኅበረሰቡ ግኝት የሆኑ ግጥሞች ለሰርግ መዋል አለባቸው ። ዜማ የዝሙት ማስታወቂያ ሲሆንና እጅና እግርን ማወደሻ ሁኖ ሲቀር ይተቻል ። መንፈሳዊነት ማኅበረሰብን የሚደፈጥጥ አይደለም ። በሰርጌ ጌታ ይክበር የሚሉ አሉ ፣ ጥሩ ነው ። ጌታ ግን የሚከብረው በሁለት ሰዓት ፕሮግራም ብቻ ሳይሆን በኑሮ ውስጥ ነው ። ሚስትህን በአጋፔ ፍቅር ስትወዳት ፣ ባልሽን እንደ ራስ ስታከብሪው ያን ጊዜ እግዚአብሔር ይከብራል ።
በዜማ መለቀስ ፣ ኀዘን መተንፈስ አለበት ። ያልወጡ ኀዘኖች ብዙዎችን ለድባቴ እየዳረጉ ይገኛሉ ። አገራችን ታላላቅ ሰዎች የነበሩባትና ያሉባት አገር ናትና ደስታንም ኀዘንንም መግለጫ አበጅተዋል ። ደግሞም የባሕላችን ማሳያ ነውና ሊከበር ይገባዋል ። አለማልቀስ ዘመናዊነትም መንፈሳዊነትም አይደለም ። ሬሳ አስቀምጦ አላለቅስም ማለት ጉራ ሲሆን አብረው የሚያላቅሱ ሲሄዱ ውጋቱ ይጀምራቸዋል ። እንዴት ሰው ሞትን እያስተናገደ ለማልቀስ ይሳሳል ?
አገርን የሚያወድሱ ፣ ጀግንነትን የሚያነሣሡ ዜማዎች አንድን ትውልድ የአገር ዘብ አድርጎ የማቆም አቅም አላቸው ። እዚህ የምንጽፈውና የምናመልከው በዳር ድንበር የሚጠብቅ ወታደር ስላለ መሆኑን ማወቅና ክብር መስጠት ይገባናል ። ከዜማ ጋር የዜማ መሣሪያዎችን መለማመድ ግድ ይላል ። ቢያንስ አንድ የዜማ መሣሪያ ማወቅ ለቀጣዩ ዕድሜ ፣ ለእርጅና ብቸኝነት ወሳኝ ነው ። ዜማ ለማኞች እንኳ ጨካኙን የሚያራሩበት ነው ። የዜማ ዕቃ ይዘው የሚያዜሙም ከመንገዳችን ቆም ያደርጉናል ። ዘወትር ከጸሎታችን ጋር ድምፅ አውጥተን ብንዘምር ላሉብን ውጥረቶች ቅለት ይሰጠናል ። ነገር ግን አጠገባችን ያለውን ሰው እንዳንረብሽ ፣ ተወዳጁን አምላክ በእኛ ረባሽነት እንዳናስጠላው መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። ዜማ የራሱ ሥርዓት አለውና ሊጠና ፣ ሊያድግና ሊበረታታ ይገባዋል ። ከሕይወት ሥነ ሥርዓት አንዱ ዜማ ማዜም ነው ። በቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት የዜማ ዕቃ ጸናጽል ፣ መቋሚያና ከበሮ ነው ። የምእመናን የዜማ ዕቃ በገና ፣ መሰንቆ ፣ ክራር ፣ እንዚራ ተጠቃሽ ናቸው ።
ይቀጥላል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ.ም.